Sunday, August 9, 2015

የኢህአዴግ ምክር ቤት የ10ኛው ድርጅታዊ ጉባኤ ረቂቅ ሪፖርትን ገምግሞ ለጉባኤው እንዲቀርብ በመወሰን መደበኛ ስብሰባውን አጠናቀቀ

የኢህአዴግ ምክር ቤት ከነሃሴ 1-2 ቀን 2007 ዓ.ም ባካሄደው መደበኛ ስብሰባው  የመጀመሪያውን የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን እቅድ አፈጻጸምና የ9ኛው የኢህአዴግ ጉባኤ ውሳኔዎች መሰረት በማድረግ የተዘጋጀውን ረቂቅ ሪፖርት በዝርዝር በመገምገም ለ10ኛው የድርጅቱ ጉባኤ እንዲቀርብ መወሰኑን የኢህአዴግ ምክር ቤት ጽሕፈት ቤት አስታወቀ፡፡
የመጀመሪያው የእድገትና ትራንስፎርሜሽን እቅድ ለሁለተኛው የእቅድ ዘመን መነሻ የሚሆኑ ልምዶችና ትምህርት የተገኘበት መሆኑን የገመገመ ሲሆን በእቅድ አፈጻጸሙ የነበሩ ስኬቶችን ለማስፋት እንዲሁም የነበሩ ችግሮችንና ተግዳሮቶችን ትኩረት ሰጥቶ ለመፍታት የተደረገውን ርብርብ ተኩረተ ሰጥቶ ተወያይቷል። የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ አፈፃፀሞችን በዝርዝር የገመገመው ምክር ቤቱ በመጀመርያዎቹ አራት አመታት የ10 ነጥብ 1 በመቶ የተመዘገበ  መሆኑን የገመገመው ምክር ቤቱ  እድገቱ ሀገራችን በአለም አቀፍ ደረጃ  እጅግ ፈጣን ዕድገት እያስመዘገቡ ካሉ ጥቂት ሀገራት አንዷ እንድትሆን ያስቻለ ስኬት መሆኑን አረጋግጧል።
የእድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅዱን የልማት ሃይሎችን በተቀናጀና በተደራጀ መልኩ በማንቀሳቀስ በልማት ሰራዊት ግንባታ አቅጣጫ መፈጸሙ ስኬታማ አፈጻጸምና እንዲኖርና የልማት ሃይሎች ዓቅም ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጎለበተ እንዲመጣ ያደረገ በመሆኑ ተጠናክሮ መቀጠል እንደሚገባው ምክር ቤቱ አስምሮበታል።
በገጠር የልማት ሰራዊት ግንባታው  በተለይም በተፈጥሮ ሃብት ልማት በየዓመቱ በሚልዮኖች የሚቆጠር ህዝብ አካባቢውን ለማልማት ያደረገው ርብርብ ውጤታማና ለቀጣይ ስራም የተሻለ ልምድ የተገኘበት መሆኑን የተመለከተው ምክር ቤቱ በመስኖ ልማትም እያንዳንዱ አርሶ አደር አማራጭ የውሃ ዕቀባ ዘዴ እንዲኖረው ለማድረግ የታየዘው ዕቅድ አፈፃፀም በሚፈለገው ደረጃ ባይሆንም በአጠቃላይ የመስኖ ስራው ግን ለቀጣይ ስራ ትምህርት የተገኘበት እንደሆነ ምክር ቤቱ አይቷል። በገጠር በሌሎች የትምህርትና የጤና ልማት መስኮችም የሰራዊት ግንባታውን አጠናክሮ ለማስቀጠል የሚያስችል ሰፊ ልምድ የተገኘበት በመሆኑ ለቀጣይ የዕቅድ ዘመን አመቺ ሁኔታዎች መፈጠራቸውን ገምግሟል። በከተማ የልማት ሰራዊት ግንባታ ረገድም በትምህርትና በአነስተኛና ጥቃቅን ተቋማት መስኮች በመልካም ተሞክሮነት የሚወሰድ ሆኖ የህዝቡን ተሳትፎና ተጠቃሚነት መሰረት ያደረገና በቀጣየ ተጠናክሮ መቀጠል ያለበት አፈፃፀም መመዝገቡን በዝርዝር የፈተሸው ምክር ቤቱ በመልካም አስተዳደር ረገድ በተለይም በሲቪል ሰርቪስና በፍትሕ መስክ ግን የተመዘገበው መሻሻል እንደተጠበቀ ሆኖ የህዝቡን እርካታ ያላረጋገጠ በመሆኑ የታዩ ጉድለቶች በቀጣይ ትኩረት የሚሻ እንደሆነ ምክር ቤቱ አፅንኦት ሰጥቶ ተወያይቶበታል።
ባለፉት 12 ዓመታት የተመዘገበውን ፈጣን፣ ተከታታይና በየደረጃው የህዝቡን ተጠቃሚነት እያረጋገጠ የሚገኘውን እድገት ለማስቀጠል የኢኮኖሚው መዋቅራዊ ለውጥና ትራንስፎርሜሽን የቀጣይ ትኩረት እንደሚሆንና በማኑፋክቸሪንግና በኤክስፖርት ንግድ የነበረው ዝቅተኛ አፈፃፀም ትኩረት ሰጥቶ ሊፈታ እንደሚገባ ምክር ቤቱ አፅንኦት ስጥቶበታል።
የዴሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታ አፈፃፀምን በዝርዝር የገመገመው ምክር ቤቱ የዴሞክራሲ ስርዓታችን ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጎለበተ መጥቷል ብሏል። በዴሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታ ስራው ምሶሶ የሆኑት የህዝብ ምክር ቤቶች ሕግ የማውጣትና አስፈፃሚውን አካል የመቆጣጠር ዓቅም በቀጣይነት እየተሻሻለ የመጣ ቢሆንም በቀጣይ ህዝቡን ይበልጥ እያሳተፉ ለመሄድ ርብርብ እንዲያደርግና ለምክር ቤቶች ተጠሪ የሆኑ ዴሞክራሲያዊ ተቋማት፣ ህዝባዊ ማሕበራት፣ ሚዲያና የመሳሰሉ ተቋማት ለዴሞክራሲያዊ ስርአት ግንባታ ሚናቸው ይበልጥ ሊጠናከር እንደሚገባ ተመልክቷል።
አምስተኛው ጠቅላላ ምርጫ ከፍተኛ የህዝብ ተሳትፎ በተረጋገጠበት ነፃ፣ ፍትሃዊ፣ ዴሞክራሲያዊና ሰላማዊ ሆኖ መጠቃለሉን የተመለከተው ምክር ቤቱ ህዝቡ ለኢህአዴግ የሰጠውን ከፍተኛ ኃላፊነት በብቃት ለመወጣት መላ የድርጅቱ አመራርና አባላት በቁርጠኝነት ሊንቀሳቀሱ እንደሚገባ አስምሮበታል፡፡ የመድብለ ፓርቲ ዴሞክራሲያዊ ስርዓቱን ይበልጥ አሳታፊ በማድረግ አጠናክሮ ለማስቀጠል የምክር ቤቶችና የዴሞክራሲ ተቋማትን አቅም የማጎልበትና የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤትን በማጠናከር የፓርቲዎቹን ተሳትፎ ማረጋገጥ በቀጣይ ትኩረት ሊሰጠው እንደሚገባ ገምግሟል።

በመጨረሻም ምክር ቤቱ በያዝነው ወር የሚካሄደው የኢህአዴግ 10 ድርጅታዊ ጉባኤ የሚቀርበውን ሪፖርት በመጀመርያው የእድገትና ትራንስፎርሜሽን እቅድ አፈጻጸም የተገኙ ልምዶችን መነሻ በማድረግና ህዝቡ በ5ኛው ጠቅላላ ምርጫ ለኢህአዴግ የሰጠውን ከፍተኛ ኃላፊነት መሰረት በማድረግ በቀጣይ አመታት የላቀ እድገትና ትራንስፎርሜሽን ለማረጋገጥ የሚያስችሉ ዋናዋና አቅጣጫዎችን አካቶ የተዘጋጀ መሆኑን በማረጋገጥ በምክር ቤቱ ውይይት ወቅት የተነሱ ሃሳቦችን አካቶ ለጉባኤው እንዲቀርብ በመወሰን ስብሰባውን ማጠናቀቁን የኢህአዴግ ምክር ቤት ጽሕፈት ቤት በላከው መግለጫ አስታውቋል።

Tuesday, August 4, 2015

A self-confident incumbent


Reda’e Halefom is head of Public Relations Directorate at the office of the Ethiopian Peoples' Revolutionary Democratic Front (EPRDF) Council.

Reda’e earned his BA degree in Sociology and Social Anthropology from Addis Ababa University. He then started working at different local-level administrations in the Tigray Regional State. He was also head of the then Tigray Information Bureau branch offices  in one of the woredas. He served as a communications expert at the Government Communication Affairs Office between 2009 and 2014. He has been serving as head of the Public Relations of EPRDF since 2014. Solomon Goshu of The Reporter caught up with Reda’e to discuss the EPRDF’s election preparation and related issues. Excerpts: 
The Reporter: How are you preparing for the upcoming May 24 election?
Reda’e Halefom: As usual, EPRFD goes to elections well prepared. We started the preparations by devising an election strategy. The political parties’ code of conduct proclamation is incorporated into our election strategy. We have devised an implementation plan to guide us through the election process. In preparation, we have also given our party members and high-level political leaders special trainings. At the same time, we have started our formal election campaign process, and it looks to be going well. 
Though the first generation of the Growth and Transformation Plan (GTP I) is yet to be evaluated, your party is using the second generation of this plan in its election campaign. So, is GTP II what your party is offering to the voter public in the upcoming election?
To begin with, EPRDF is a peoples’ party. Basically, peoples’ parties do not campaign on the basis of verbal promises. In our view, campaigning on the basis of promises like ‘I do this and that’ is not healthy. We prefer to inform the voter of what we have achieved; we tend to focus on actual results. So, we speak of the things that we have done on the ground, thus far. We believe that the people have given us a contract. So, we are striving not to default on that contract. Among other things, the leadership of the party has helped the country to be among the few ones in the world registering the highest economic growth figures during the past few years. We are trying to incorporate stakeholders’ feedback into this process. Hence, our election campaign is focused on our success and failures of delivering these development activities. The whole purpose of GTP I and other plans and programs in the country is to ensure the renaissance of Ethiopia. The ruling party is working around the clock to make sure this is a reality. However, we do not like to deceive the public by promising to do this and that. 
The ruling party is repeatedly accused of mixing party and state functions. Especially during election times, the party is said to be portraying achievements that belongs to the government as its own. What do you say to that?
We take such criticisms for their mere value as criticisms. But, we have to evaluate whether such claims have any grounds, or any piece of evidence to back them. Anywhere in the world, the government executes the ruling party’ political programs and strategies. This is a normal procedure. In the more seasoned democracies, you will see frequent change in the ruling parties based on the periodical elections they hold. This would help to clearly draw the line between the ruling party and the government. Apart from the ruling party and the government operators themselves, the public is also well aware of the demarcation that exists between the two. However, it does not mean that in Ethiopia party and government lines cross one another all the time. This ruling party is very watchful of that line. Even when there is an overlap it is will be done via legal and democratic ways. Sometimes, problems might exist on both organizational and individual levels; and this demarcation might be breached. But when it happens, the party takes measures to correct them. Nevertheless, we can’t say that the ruling party and the government should never meet. It’s the leaders of the ruling party that establishes a government. They are expected to have clearly distinct roles in government and the party. Although there are some who might get confused about these distinct roles, the party clearly knows their responsibility. On the other hand, it is the policies and strategies of the ruling party that have brought the positive outcomes we see today. So I see no reason why the party should not advertise these success stories and use them in election campaigns. 
It is said that sheer numbers (membership) is one strength that the ruling party has over the other parties in Ethiopia. In this regard, coming into the election, what is the final tally of your party membership? How far are these members devoted to the party?
Currently we have more than six million registered members. Although we believe that the people are the ones responsible for the nation’s destiny, we also think that all six million members do have their own irreplaceable role to play. These (EPRDF members) are people who are devoted to make the future of their country better. Nevertheless, I do admit that there might be a few individuals who don’t share this vision; and that they joined the party for totally the wrong reasons. For instance, there might be a few who are after their own benefits. They expect that they would benefit from being members of the party, but most of them find out that this is not the case and opt to leave immediately. The party also tries to filter its members. The first thing we do is try and support them to know exactly what is expected from them as members of EPRDF. We offer them continuous training sessions and try to build their capacity. Our main training machineries are those lower-level party organs. They are the major training and research cells. Apart from that, we organize various forums and meetings where members can exchange ideas and hold ideological debates among themselves. Nevertheless, if all this could not shape the members and that it has problem internalizing what party is all about, then members would be let go. 
The oppositions accuse of you narrowing down the political playing field. They say your financial might has a lot do with that. Do you think EPRDF’s financial capacity has a role to play in its success in dominating the political scene?
EPRDF’s source of strength is never its financial resources. It is rather the clarity of its political direction. It is because our policies are concrete and are home-grown solutions. Our policy direction is instrumental in making poverty and backwardness history in Ethiopia. When you have a political direction like this, it is bound to be the case that the people would rally behind you. On the other hand, a political party needs to make its policies and programs known to the voter public and try to garner support on the basis of political programs. I would say the opposition is quite weak in this regard. Most of opposition politicians become visible to the voter public around election time. They need to understand politics is a full-time job. I don’t think this weakness of theirs should be covered up by lack of financial capacity. Yes, it is important that the government offers financial support to fill this gap. However, subsidy alone cannot be an adequate budget to a fully functioning political party. They need to expand their support base and raise better financial resources from their members. If you talk about subsidy to political parties, it was started fairly recently in Ethiopia. Before that, there were political parties operating in Ethiopia. I do understand there could be a few parties who are facing real financial strain to operate as a party. However, we also know that some parties use finance as an excuse; in fact we know many of them get a lot of unaccounted for and shady looking financial contributions. 
So, are you telling me that the political playing field poses no impediment to the parties that it is their own political direction that is to blame?
Yes. My party and I are convinced that, for political forces with the right political vision and direction, there is adequate political space in Ethiopia. It is possible to bring about changes in Ethiopia. The door is not closed. If you look at the member parties of the ruling front (EPRDF), they started their struggle with nothing but the right political direction and vision. They went ahead to overthrow that system with millions behind them. Of course, I cannot conclude that all the opposition parties share the same weaknesses. But, I can say that most of them fail in the sense that they don’t exploit the five-year period between elections. They tend to come to life during an election year. Most of them spend their pernicious time going from one embassy to the other instead of going down to the people and mobilizing mass support. Even if we say that the political playing field is constricting, they have space to change that through peaceful struggle. 
Political commentators argue that the Ethiopian political land- scape is tinted with highly polarized views. Do you agree with that assessment? Is the ruling party immune to this syndrome?
In our view, we do see significant changes in Ethiopian politics. We have come a long way since those days where different political opinion can cost one their life. After the fall of Derg, forces that were defeated in the arms struggle have revived their extreme political agenda via various means such as the media. I still believe that we are seeing significant improvements in this regard compared to the early days of the ruling party assuming power. However, the improvement is not because these forces have changed their ways but rather because the people have said that they had enough of extreme politics in Ethiopia. So, some of them were forced to reconsider their extreme political agendas. Still very few have decided that there is no better option than peaceful and legal political struggle. There are parties  that  abide by the political parties’ code of conduct and have become part of the political parties’ joint council. This has neutralized the extremely polarized political environment in Ethiopia. This is a success by itself. Nevertheless, there are still those who choose to pursue the extreme and illegal ways. There are those who are calling terrorist groups heroes. As far as we are concerned, we believe we are part of the solution to neutralize the extremely polarized political environment in Ethiopia. We are not sources of extremisms ourselves. 
How successful is this political parties’ Joint council? What are its achievements since its formation in 2010?  Does the fact that some of the major opposition forces in Ethiopia are not part of this Council have an impact on its activities?
First of all, we have to ask who said these political parties are the major opposition voices in Ethiopia. We see all opposition parties as equals. What makes the ruling party different is the fact that it is ruling the nation at this time. Actually, the council is doing quite well. To begin with, the council incorporated political parties which have chosen to pursue peaceful and legal political struggle in Ethiopia. The council mainly entertains complaints of the parties and addresses their problems. Apart from addressing these issues, the council draws lessons from these cases. The council entertains various ideas and conducts heated debates around issues. Finally it endorses those ideas which have managed to gain consensus among members of the council. Indeed, it still can do much better. But, we believe that it is a big step forward that they were able to sit down together and discuss issues of national importance at this level. 
In your view, which party is a formidable opposition and is a worthy competition for the ruling party?
We believe our main challenge comes in the form of poverty and backwardness. We neither wish to single out nor have the basis to select one or two parties and say that they are our main competition. I cannot imagine considering political parties which do not even have adequately clear ideologies as a strong opposition. We are more worried about our own weaknesses.
Recently some legal issues have been raised against your party by your opponents. The gist of the matter is that EPRDF is made of four member parties but not individuals; and that these member parties are regional parties which cannot be allowed to field candidates in federal cities like Addis Ababa and Dire Dawa. What do you say to that?
This complaint was tabled by the Blue party in a letter that it has written to the National Electoral Board of Ethiopia (NEBE). To begin with, it is very odd that the Blue party has tabled its concern to a body that it accuses of being influenced by the ruling party. Furthermore, it is also odd that the complaint is about the ruling party that it says has a strong hold on the Board. EPRDF is a party that is registered as a national party. Its member parties are regional parties. So, the party is eligible to any privileges that is afforded to any national parties in Ethiopia. Both the capital city and Dire Dawa are federal cities. There is nothing on its bylaws that restricts it fromtaking part in the election in federal cities. The real issue here is  the reasons behind this Blue party’s complaint. It is a desperate ploy to get itself out of the mess that it is in. For one, its nine-party coalition was not able to get accreditation from the NEBE. On the other hand, it tried to field candidates who are registered under a different political party. This too was rejected by the Board. So, the complaint was nothing more than a tactic to divert its own misgivings and shortcomings. 
Political commentators and some parties in the opposition camp identify the political parties registration law, the press law, the civil society proclamation and the anti-terrorist proclamations to be undemocratic and contrary to the constitution itself. Did your party have any plans to reconsider these laws should you be elected for another term in office?
It is clear that extreme neoliberals and local opposition forces have joined forces around these above-mentioned laws and proclamations. We know who is echoing whose agenda here. These are criticisms which are not advanced for the benefit of the people. If you see it, the civil society proclamation is all about using the financial resources accessed by the civil society organizations to development purposes; and nothing else. In fact, since the proclamation, civil society organizations have increased in number in Ethiopia. The criticism against the press law is also quite clear. It is because the industry is closed to foreign investors. We know that. Of course, the anti-terrorism proclamation as well has some groups worried: the parties that are actually arguing that Ethiopia is not facing terrorism threats. It will suffice to see our neighbors like Kenya, if we have not foiled a number of terrorist plots against the country.
The other criticism against your party is your view towards constitutional amendment. They say the ruling party sees constitutional amendment as the dismantling of the whole system. Nevertheless, the constitution does have its own constitutional amendment procedure. But, why did the ruling party tend to be sensitive when it comes to constitutional amendment?
First of all it should be clear that the FDRE constitution is not EPRDF’s or any other bodies’. Rather it is a declaration of the people; I do not think it is healthy to tell the people that its constitution needs to be amended. When have the people asked for a constitutional amendment? If the request comes via the proper channels, EPRDF is first to back that process. However, the party does not wish to initiate amendments unilaterally.
After the 2010 election, the ruling party has officially adopted the developmental state model and its system of governance. Is it a substitute for revolutionary democracy or are the two being considered side by side?
EPRDF’s official direction is developmental democracy. Revolution is the nature of development and democracy. So, the revolutionary nature combines both development and democracy. The two have to be balanced to bring about a basic change. The government should play its role in filling the market gap that the private sector could not fill. This makes it developmental. The nature of the country by itself, which is diversity, calls for a democratic form of governance so that all are recognized and respected. So, both are in there together. The EPRDF is still a revolutionary front. 
But commentators say that developmental state model is rather a growth model; not a political ideology. They argue that this is not a party ideology. What do you say to them?
Yes, I have heard that argument before, and I think,it is a view that is advanced by someone who is not well-versed in the subject matter. Or,it is deliberately concocted by someone to mislead the general public regarding the political direction that the ruling is pursuing. Take any developmental state, it is ruled by a political party at the end of the day. The government implements the party ideology, whether one likes it or not. So, you can see that this arguments do not carry any weight.
Your party said before that this would be the election where most of the old guards would leave the party leadership and make way for new generation of leaders. Is it going to happen now?
Succession is a process not an event. One generation can go as far as a few years in leading the party. So, succession plays an irreplaceable role in carrying the party forward because, across generations, the public would have a different set of demands and development aspiration. So, the leadership of the party has to evolve to keep up with that changing reality. However, this is a process and there are no plans to finish or start the succession process during this year’s election or the next. 
You constituted an overwhelming majority in the lawmaking body during the last five years; you and your affiliate parties held all but two seats in the parliament. So, what are your plans for this election?
During last election the opposition were barred from entering parliament by the public. The public has spoken through its voting card. Personally, I don’t think there are parties which, let alone can compete, can stand on an equal footing with EPRDF. Nevertheless, we think it is for the public to decide and we leave it at that.
 Source
http://www.thereporterethiopia.com/index.php/interview/item/3345-a-self-confident-incumbent

የቤት ስራችንን በመስራታችን የተሰጠን እውቅና


ከአሜሳይ ከነዓን
የጥንታዊ ስልጣኔ ባለቤት የሆነችው ኢትዮጵያ  በማናቸውም ጊዝያቶች በውጭ ወራሪ ሃይላት ያልተንበከከችና ለዘመናት ሉአላዊነቷን ጠብቃ የቆየች ሀገር ናት። ሁሉም የአፍሪካ ሀገራት በቅኝ ግዛት ስር በወደቁበት ጊዜም ከየአቅጣጫው የተደቀኑባትን ወረራዎች በብቃት በመመከት የራሷን ሉአላዊነት ከመጠበቅ ባሸገር ለሌሎች የነፃነት ታጋዮችም የአይበገሬነት ተምሳሌት በመሆን ታግሎ ማሸነፍ እንደሚቻል በተግባር ያስተማረች ነች ሀገራችን።

የኢትዮጵያና የአሜሪካ ሁለትዮሽ ግንኙነትም የተጀመረው አብዛኞቹ የአፍሪካ ሀገራት በቅሽ ግዛት ስር በነበሩበት ዘመን ነበር፡፡ እናም ግንኙነቱ እ.አ.አ ከ1903ዓ.ም ጀምሮ አንዴ ዝቅ ሌላ ጊዜ ደግሞ ሞቅ እያለ መጥቶ በአምባገነኑ የደርግ ስርዓት በጎሪጥ እስከመተያየት ደርሶ ነበር። ለዚህ ግንኙነት መቋረጥ ደግሞ ደርግ የተከተለው የተሳሳተ የውጭ ግንኙነት አቅጣጫ ሲሆን ይህም ስርዓቱ የሶሻልዝም ርእዮተዓለም እከተላለሁ በማለት የጀመረው ፀረ-አሜሪካ ፕሮፓጋንዳ ነበር።
ከደርግ ወድቀት ማግስት በዴሞክራሲያዊ ሁኔታ ህዝባዊ  ስልጣን የተረከበው ኢህአዴግ በጋራ ጥቀም ላይ የተመሰረተና ማንንም በወዳጅነት ማንንም በጠላትነት የማይፈርጅ የውጭ ግንኙነት ፖሊሲ በመቅረፅ ኢትዮጵያ ከአለም ሀገራት ጋር ያላት ግንኙነት በእኩልነትና በመከባበር ላይ እንዲመሰረት እልህ አስጨራሽ ትግል አድርጓል።ከአሜሪካ ጋር ለ17 ዓመታት ያክል ተቋርጦ የነበረውንም ግንኙነት በተሻለ ሁኔታ በማስቀጠል እንዲጠናከር አድርጓል፡፡

ሀገራችን ራሷን በምስራቅ አፍሪካም ይሁን በመላው አለም ለቱሪዝምና ለኢንቨስትመንት የተመቸች፣ በተለያዩ የዓለማችን አካባቢዎች የሚገኙ ባለሃብቶች መዋእለንዋያቸውን  ኢንቨስት ለማድረግ የሚመርጧትና በተለይ ወትሮ ትታወቀበት ከነበረውና ሁሉንም ኢትዮጵያዊ አንገት ከሚያስደፈው የረሃብ፣የኋላቀርነትና የጦርነት ታሪኳ ተላቃ በራሷ ዓቅም መቆም የምትችል ዴሞክራሲያዊት ሀገር ለመገንባት ባለፉት ሁለት አስርት አመታት ያለመታከት ተሰርቷል፡፡

ኢህአዴግ በቀየሳቸው ትክክለኛ ተኮር ፖሊሲዎችና ስትራቴጂዎች ከራሳችን አልፈን አለም በእኛ ለውጥ እንዲያምን ያስገደደ ፈጣንና ተከታታይነት ያለው ፍትሐዊ እድገት ተመዝግቧል፡፡ አገራችን ከፈጣን እድገቷ ባሻገር የተረጋጋና ዘላቂ ሰላም ያለባትም አገር ለመሆን በቅታለች፡፡ ከውስጣችን አልፈን የፍሪካውያን ወንድሞቻችንን ሰላም ለመጠበቅም ከፍተኛ መስዋእትነት እየከፈልን ያልተቆጠበ ጥረት በማድረግ ላይ እንገኛለን፡፡

ይህ ሁለንተናዊ ለውጣችን ታዲያ ሀገራችን ስሟ በዓለም አቀፍ መድረኮች የሚጠራው በተመፅዋችነቷን ሳይሆን በልማት አጋርነቷንና በኢንቨስትመንት መዳረሻነቷን እንዲሆን አስችሏል። የወጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት በመሳብ ረገድም አሁንም ብዙ መስራት የሚጠበቅብንና ከዘርፉ የተሻለ ጥቅም ለማግኘት የሚያስችለን ምቹ ሁኔታ መፍጠር ያለብን ቢሆንም እስካሁን የተገኙ ልምዶችን ግን ሀገራችን የሚያበረታታ ውጤት በማስመዝገብ ላየ ትገኛለች።  ዛሬ የቱርክ፣ ህንደና ቻይና ግዙፍ ኩባንያዎች ባሻገር የአውሮፓውያንና የአሜሪካዊያን ባለሃብቶችንም በአገራችን መዋለ ነዋያቸውን በማፍሰስ ላይ ይገኛሉ፡፡ ይህ ሁሉ ደግሞ በተከተልነው ትክለኛ የዕድገት አቅጣጫ የተገኘ ስኬት ነው።

አገራችን ኢትዮጵያ የተለጠጠና ወደተሻለ የእድገት ምዕራፍ ሊያሸጋግረን የሚችል የአምስት ዓመት የእድገትና ትራንስፎርሜሽን እቅድ በማውጣት የምእተ ዓመቱን  የእድገት ግቦች እንዲሳኩ ከማንም በላይ በቁርጠኝት በመትጋት ላይ ያለች ሀገር ናት፡፡ በዚህም በምእተ ዓመቱ  የእድገት ግብ የተቀመጡ ተግባራትን  በማሳካት ዓለም በአንድ ድምፁ ቁርጠኝነቷን እንዲመሰክርላት ሆኗል፡፡ የህፃናት ሞትን ለመቀነስ የተያዘውን እቅድ ቀድማ አሳክታለች፡፡ የእድገት ግቡ መጀመሪያ ላይ የነበረውን የ46 በመቶ የድህነት መጠን ወደ 22 በመቶ በማወረድ በርካታ ሚሊዮን ዜጎቻችን ከድህነት አረንቋ እንዲወጡ በማስቻል አንፀባራቂ ድል ተመዝግቧል፤ አሁንም የእነዚህ በድህነት ውስጥ የሚኖሩ ዜጎቻችን ህይወት ለመለወጥ ቀጣይ ርብርብ ማድረግ ያለብን ቢሆንም፡፡

ይህ ሁሉ የሚያሳየው አገራችን ከድህነት ለመላቀቅ ያላትን ቁርጠኝነት ነው፡፡ ለዚህም ነው በዓለም አቀፍ ደረጃ ከኢትዮጵያ ጋር በአጋርነት መስራት እንደ ጥሩ አጋጣሚ እየተወሰደ ያለው። የተለያዩ አለምአቀፍ መድረኮችን በማዘጋጀት እውቅናን ያተረፈችው አገራችን በያዝነው በ2007 ዓ.ም  ሶስተኛውን አለምአቀፍ የፋይናንስ ለልማት ጉባኤ በማዘጋጀትም አቅሟንና የልማት አጋርነቷን በተግባር አረጋግጣለች፡፡ የተመድ ኢኮኖሚና ማህበራዊ ጉዳዮች ጀነራልና የሶስተኛው አለምአቀፍ የፋይናንስ ለልማት ጉባኤ ሴክሬታሪ ጀነራል ዉ ሆንግቦ ጉባኤው ከመካሄዱ በፊት በኢትየጵያ የሚካሄደው ጉባኤ ተገቢነቱን በማመላከት በአገሪቱ እየተመዘገበ ያለው ፈጣንና ተከታታይነት ያለው ፍትሐዊ እድገት ጉባኤን በስኬታማነት እንድታዘጋጅ ያግዛታል ሲሉ ተደምጠዋል፡፡

በእርግጥም ከኳታርና ከሜክሲኮ በኋላ በሶስተኛናት አገራችን የአለም አበዳሪ ተቋማትና መሪዎች የተገኙበትን ጉባኤ በስኬታማነት በማጠናቀቅ ያለችበትን ሁለንተናዊ የለወጥ ቁመና በተጨባጭ ማሳየት ችላለች፡፡ የሐምሌ ወር የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ባራክ ሁሴን ኦባማ ጉብኝትም ይህችን አለም ለውጧን እየመሰከረላት ያለችውን ብሩህ ተስፋዋን ፍንትው ብሎ የሚታየው አገር እውቅና መስጠት ተገቢና ወቅታዊ ነው የሚል እምነት አለኝ፡፡ የፕሬዝዳንቱም ይፋዊ ጉብኝት የኢትዮጵያና የአሜሪካ ስትራቴጂክ ግንኙነት ሁለቱንም አገራት የሚጠቅምና በመተማመንና መደጋገፍ ላይ የተመሰረት እንዲሆን የሚያግዝ ነው፡፡


አሜሪካ በሀገራችን እየተመዘገበ ያለው ሁለንተናዊ እድገት አስተማማኝና ቀጣይነቱም የማያጠራጥር እንደሆነ በማመኗ ግንኙነቷን ማጠናከሯና ለሀገራችን ለውጥም እውቅና መስጠት ተገቢ ነው፡፡ በአገራችን ባለፉት ዓመታት የተዘመገቡት የሰላም የልማትና የዴሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታ እመርታዎች አሜሪካን ጨምሮ በርካታ ሀገሮች ሀገራችንን ተመራጭ እንዲትሆን አስችሏል፡፡ ይህ ማለት ግን ሁሉ ነገር አበቃለት ማለትም አይደለም፡፡ በጀመርነው ፍጥነት በመቀጠል ሀገራችን ከድህንት ተላቃ መካከለኛ ገቢ ካላቸው ሀገራት ተርታ ማሰለፉ በከፍተኛ ቁርጠኝነት መስራታችን አጠናክረን መቀጠል ይኖርብናል። ኦባማ በጉብኝታቸው ወቅት እንደገለፁት 100 ፐርሰንት ትክክል የሚባል ዴሞክራሲ የትም የለም፤ በሀገረ አሜሪካም ቢሆን፡፡ ለውጡም እንዲሁ በአንድ ጀምበር ዳር ማድረስ አይቻልምና ሁሉም የራሱን ጊዜና ጉልበት ይፈልጋል፡፡ የሀገራችን አርሶና አርበቶ አደሮች፣ ኢንዱስትሪያሊስቶች፣ ባሃብቶች፣ ወጣቶችና ሴቶች ሁሉም በጋራ ሲተባበሩ ነገ ከበድ ያለውን የቤት ስራ ከመስራት የሚያግዳቸው አንዳች ሃይል እንደሌለ የእስካሁን ስኬታቸው ዓይነተኛ ማሳያ ተደርጎ የሚወሰድ ነው። ዛሬ ትናንት ያሰፈርነውን የቤት ስራችንን በአግባቡ በማጠናቀቃችን አለም ድጋፉን እድገታችንን እውቅና በመስጠት እያሳወቀን ነው፡፡ ነገ ደግሞ የተሻለችሀገር፣ የተሻልን ህዝቦች ሆነን በዓለም አደባባይ አንገታችን ይበልጥ ቀና ለማድረግ አሁንም እንደ ትናንቱ ልማት፣ ሰላምና ዴሞክራሲ የህልውናችን መሰረቶች ናቸው ብለን ከፍተኛ ርብርብ ማድረግ ይኖርብናል፡፡ ሰላም፡፡       

Tuesday, May 5, 2015

ኢህአዴግ በተከተለው ትክክለኛ የትምህርት ፖሊሲ የዜጎችን ፍትሃዊ ተጠቃሚነት ማረጋገጥ ያስቻሉ ስኬቶች ተመዝግበዋል!!

የተከበራችሁ የአገራችን ህዝቦች፣
ዜጎች ሊሟሉላቸው ከሚገቡ መሰረታዊ መብቶች ውስጥ የመማር መብት አንዱ ነው፡፡ የአንድን አገር ኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካዊና ማህበራዊ ልማት ለማረጋገጥ ትምህርት ቁልፍ መሳሪያ ተደርጎ ይወሰዳል። ወደ ኋላ መለስ ብለን ከ1983.ም በፊት የነበረውን የአገራችንን የትምህርት አቅርቦት ስንቃኝ በበርካታ ችግሮች የተተበተበ ነበር፡፡ የትምህርት አቅርቦቱ በተደራሽነትም ሆነ በፍትሃዊነት እጅግ ከፍተኛ ችግር ነበረበት፡፡ በ1983ዓ.ም ዕድሜያቸው ለትምህርት ከደረሱ ህፃናት መካከል 19 በመቶው ብቻ ነበሩ ከ1ኛ እስከ 6ኛ ክፍል የመማር ዕድል ያገኙት፡፡
የአገራችን የትምህርት ስርዓት ችግር ግን አገልግሎቱ በሚገባ ያልተስፋፋ መሆኑ ብቻ ሳይሆን በፍትሃዊነትም ከፍተኛ ችግር ነበረበት። በከተማና በገጠር፣ በወንዶችና በሴቶች እንዲሁም በብሄር ብሄረሰቦች መካከል የነበረው ስርጭትና ተሳትፎ በእጅጉ የተዛባ ነበር። ዜጎች በአፍ መፍቻ ቋንቋቸው የመማር እድላቸውን የተነፈጉባቸውን ስርዓቶች ነው ያሳለፍንው።
ኢህአዴግ በድርጅታዊ ፕሮግራሙ ደረጃውን የጠበቀና ከአገሪቱ የልማት አቅጣጫዎች ጋር የተቆራኘ ትምህርትና ስልጠና ማስፋፋት እንደሚገባ በማስቀመጥ የአገራችን ተጨባጭ ሁኔታ ያገናዘበ የትምህርት ፖሊሲ ቀርጾ ተግባራዊ አድርጓል። የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርትን ለሁሉም ዜጎች ማዳረስ እንደሚገባ፣ ከኢኮኖሚ እድገቱ ፍላጎት ጋር የተጣጣመ የሁለተኛና ከፍተኛ ትምህርት ማስፋፋት እንደሚያስፈልግ ግልፅ የፖሊሲ አቅጣጫ ተቀምጦ ተጨባጭ ስኬቶች ተመዝግበዋል፡፡
የተከበራችሁ የአገራችን ህዝቦች፣
ኢህአዴግና የሚመራው ልማታዊና ዴሞክራሲያዊ መንግስት ለትምህርት ትኩረት ሰጥተው በመረባረባቸው በአሁኑ ጊዜ በሁሉም የትምህርት እርከኖች ከ24 ሚሊዮን በላይ ዜጎች በትምህርት ላይ ይገኛሉ፡፡ ይህም አብዛኛው የአገራችን ዜጎች የመማር መብታቸውን ተነፍገው የነበረበትን ሁኔታ በእጅጉ የቀየር በኢህአዴግና በአገራችን ህዝቦች ርብርብ የተገኘ ትልቅ ድል ነው፡፡ ባለፉት ስርአቶች ታፍኖ የነበረው የዜጎች በአፍ መፍቻ ቋንቋ የመማር መብት ህገ መንግስታዊ ጥበቃ ተደርጎለት በአሁኑ ጊዜ 24 በሚሆኑ የብሄር ብሄረሰብ ቋንቋዎች ዜጎች በአፍ መፍቻ ቋንቋቸው በመማር ላይ ይገኛሉ፡፡
በቅድመ መደበኛ ወይም አፀደ ህፃናት ትምህርት በ1983ዓ.ም በመላ አገሪቱ 98ሺ 412 ህፃናት ትምህርታቸውን ይከታተሉ የነበረበት ሁኔታ ዛሬ በእጅጉ ተቀይሮ በ2006ዓ.ም ወደ 2.3ሚሊዮን አድጓል። በቅድመ መደበኛ ትምህርት የተገኘውን ስኬት በማጠናከር አገልግሎቱን ይበልጥ ማስፋት እንደሚገባን ተገንዝበን በመንቀሳቀስ ላይ እንገኛለን፡፡
ኢሕአዴግ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ለሁሉም ዜጎች በነፃ መዳረስ አለበት ብሎ በቁርጠኝነት ተንቀሳቅሷል፡፡ ከፍተኛ በጀት በመመደብና የህዝብን ተሳትፎ በማረጋገጥ ለህዝቡ ተደራሽ የሆኑ ትምህርት ቤቶች ተገንብተዋል፡፡ በ1983ዓ.ም 8ሺ 434 የመጀመሪያ ደረጃ ት/ቤቶች ብቻ የነበሩ ሲሆን በ2006ዓ.ም 30ሺ 800 ደርሷል፡፡ ይህም የመጀመሪያ ደረጃ ት/ቤቶችን ለማግኘት የሚወስደው አማካኝ ርቀት ወደ 2.5 ኪ.ሜትር ዝቅ እንዲል ያደረገ ሲሆን ለበርካታ ዜጎች የትምህርት እድል እንዲያገኙ አስችሏል፡፡ በ1983ዓ.ም የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት እድል ያገኙ ዜጎች ቁጥር 2 ነጥብ 6 ሚሊዮን ብቻ የነበረው ባለፈው አመት 19.2 ሚሊዮን ደርሷል፡፡ እድሚያቸው ለትምህርት የደረሰ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ንጥር ተሳትፎ በ1983 ከነበረበት 19 በመቶ በአሁኑ ጊዜ ከ1ኛ እስከ 6ኛ ክፍል ንጥር ተሳትፎ 99 በመቶ የደረሰ ሲሆን ከ1ኛ እስከ 8ኛ ክፍል ያለው ተሳትፎም 94 በመቶ ደርሷል።  
ባለፉት 23 አመታት በተደረገው ርብርብ በሁለተኛ ደረጃ ትምህርትም ከፍተኛ ስኬት አስመዝግበናል፡፡ በ1983.416 ሺ ያህል ተማሪዎች ብቻ ያስተናግዱ የነበሩት 284 የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ቁጥር ወደ 2ሺ333 አድጎ በ2006ዓ.ም ከ2 ሚሊየን በላይ ተማሪዎች ትምህርታቸውን እንዲከታተሉባቸው ማድረግ ችሏል። የትምህርት ስራችን ለፍትሃዊ ተጠቃሚነት ከፍተኛ ትኩረት የሰጠ ነው፡፡ በከተማና በገጠር የነበረውን ፍታሃዊ ያልሆነ ስርጭት በእጂጉ ተሻሽሏል፡፡ የአርብቶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የሚያስችል አቅጣጫም በመከተል ውጤታማ ተግባራት ተከናውነዋል፡፡ የተሣትፎው መጠን እመርታዊ ለውጥ ያመጣ ቢሆንም አሁንም ወደ ትምህርት ቤት ያልመጡ ህጻናት መኖራቸው፣ መድገምና ማቋረጥ አሁንም በሚፈለገው ልክ ያልተሻገርናቸው ተግዳሮቶች መሆናቸውን ኢሕአዴግ ይገነዘባል፡፡ የቅድመ መደበኛ ትምህርት በከተሞችና በከተሞች አካባቢ የተወሰነ መሆኑም መፍትሄ የሚያሻው ነው።
ቀደም ሲል ከትምህርት አኳያ ከፍተኛ ኢፍትሃዊነት የሚታይበት ጉዳይ የሴት ተማሪዎች ተሳትፎ ነበር፡፡ ሴቶች በተለያዩ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ጫናዎች የተነሳ በትምህርት የነበራቸው ተሳትፎ ዝቅተኛ ሆኖ ቆይቷል፡፡ ለዚህም ነው የትምህርትና ስልጠና ፖለሲ ሲቀረጽ በዋነኛነት የሴቶችን የትምህርት ተሳትፎ ለማሳደግ የሚያስችሉ አቅጣጫዎችን በማካተት ተግባራዊ እንዲሆን የተደረገው። በሂደትም የሴቶች የትምህርት ተሳትፎ እያደገና ከወንዶች ጋር እየተመጣጠነ ይገኛል።
የልዩ ፍላጎት የትምህርት ፕሮግራም ተግባራዊ በማድረግም የዜጎችን የትምህርት ተጠቃሚነት በማረጋገጥ ላይ እንገኛለን፡፡ በተለያዩ ምክንያቶች በመደበኛ ትምህርት የመማር ዕድል ያላገኙ ዜጎች ከሀገሪቱ የትምህርት ስርዓት ፍትሓዊ ተጠቃሚ በመሆን የህይወት ክህሎታቸውን መገንባትና የተሻለ አምራች ዜጋ መሆን ስላለባቸው የተቀናጀ ተግባር ተኮር የጎልማሶች ትምህርት ተቀርፆ በመተግበር ላይ ነው። እስካሁን 3 ነጥብ 5 ሚሊዮን ጎልማሶች የአገልግሎቱ ተጠቃሚ የሆኑ ሲሆን 6 ነጥበብ 6 ሚሊዮን ጎልማሶች ደግሞ በመማር ላይ ናቸው፡፡
የተከበራችሁ የአገራችን ህዝቦች፣
ኢህአዴግ የትምህርት ጥራትን ለማሻሻል አጠቃላይ የትምህርት ጥራት ፓኬጅ አዘጋጅቶ በየደረጃው ከሚገኙ ባለድርሻ አካላት ጋር ሰፊ ውይይት በማካሄድ በቂ ማሻሻያና የማበልፀጊያ ግብአት በማሰባሰብ ወደ ትግበራ ተሸጋግሯል፡፡ ከፍተኛ ውጤት እያስገኘም ነው፡፡ የመማሪያ መፅሃፍትንና የመርጃ መሳሪያዎችን አቅርቦት ለማሻሻል እንዲሁም የመምህራንን መጠንና አይነት ለማሻሻል ባለፉት አመታት ከፍተኛ ጥረት ተደርጓል፡፡ ተስፋ ሰጪ ውጤቶችም ተመዝግበዋል።
በአንደኛ ደረጃ ት/ቤቶች የተማሪ መምህር ጥምርታ አንድ ለ54 በሁለተኛ ደረጃ ደግሞ አንድ ለ28 ደርሷል፡፡ በተመሳሳይ የተማሪ ክፍል ጥምርታም ለውጦች የተመዘገቡበት ነው፡፡ አለም አቀፍ ደረጃቸውን የጠበቁ የመማሪያና የማስተማሪያ መጻሕፍት በማሳተምና በማሰራጨት ተደራሽነቱ በከፍተኛ ደረጃ አድጓል፡፡ በጥምርታዎቹ የተመዘገበው ለውጥ የተሻለ ትምህርት ለመስጠትና ተማሪዎችን የበለጠ ለማገዝ አስችላል፡፡ ይሁንና ለውጡ በሁሉም ትምህርት ቤቶች ወጥነት የሌለው በመሆኑ ትኩረት እንደሚሻ ኢሕአዴግ ይረዳል፡፡
በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ረገድ ዋናው ትኩረታችን ጥራት ማስጠበቅ ላይ በማድረግ ስርዓተ ትምህርቱን ለማሻሻልና የትምህርት መርጃ መሳሪያዎችን ለማሟላት ጥረት ተደርጓል፡፡ የተገኙ ውጤቶችም ስፋት ያላቸው ናቸው፡፡ የሁለት ተቀራራቢ ዓመታትን የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ የፈተና ውጤትን ማሳያ አድርገን ብናይ እንኳ የትምህርት ጥራት እየተሻሻለ ለመምጣቱ  ዋቢ  ይሆናል፡፡ በ2002 .ም ማጠናቀቂያ የሁለተኛ ደረጃ መልቀቂያ ፈተና ከወሰዱ ተማሪዎች 2ነጥብ እና በላይ ውጤት ያስመዘገቡ 62.25% የነበረ ሲሆን ይህን ምጣኔ 2005 .ም ወደ 73.34% ከፍ ማድረግ ተችሏል፡፡ ይሁንና ችግሮቹ አሁንም ስላልተወገዱ ስርጭቱን ከኢኮኖሚያዊ እድገታችን ጋር በተቀናጀ አኳኋን የማስፋፋቱ ጉዳይ እንደተጠበቀ ሆኖ ዋናው ስራችን ጥራቱን ማሻሻል መሆን እንዳለበት ኢሕአዴግ ይገነዘባል፡፡
የተከበራችሁ የአገራችን ህዝቦች፤
ኢህአዴግና የሚመራው መንግስት ከህዝቡ ጋር በመሆን ለትምሀርት ዘርፍ ትኩረት በመስጠት በመረባረባቸው በትምህርት ተጨባጭ ስኬቶች ተመዝግበዋል፡፡ ህዝቡ በትምህርት ቤት ግንባታዎችም ሆነ በሌሎች ተግባራት የነበረው ተሳትፎ ክፍተኛ ነበር፡፡ በትምህርት ዘርፍ ለተመዘገቡ ስኬቶች መምህራን የተጫዎቱት ሚና ከፍተኛ እንደሆነ ኢህአዴግ ያምናል፡፡ የአገራችን መምህራን የሚያጋጥሟቸውን ችግሮችን በመጋፈጥ አገራቸውና ህዝባቸው የጣሉባቸውን ኃላፊነቶች በመወጣት ያበረከቱትን አስቷዋጽኦ ኢህአዴግ ከፍተኛ እውቅና ይሰጠዋል፡፡ የመማር ማስተማር ሂደት ትውልድን ለመቅረፅ ከባድ ሃላፊነት የሚጠይቅና የመጪዋን ኢትዮጵያ ዕድል የሚወስን ትውልድ በብቃት የመገንባት ጉዳይ መሆኑን በመገንዘብ ኢህአዴግ ለመምህራን ልማት ትኩረት ሰጥቶ ሰርቷል፡፡
ባለፉት አመታት የመምህራን ልማት ፕሮግራም በማዘጋጀት ሰፋፊ የአቅም ግንባታ ስራዎችን በማካሄድ ላይ ይገኛል፡፡ መምህራን የስራ ላይ ስልጠናዎች እንዲያገኙ በማድረግ አቅማቸውን ለመገንባት ጥረት ተደርጓል፤ በመደረግም ላይ ነው፡፡ ለመምህራንን የሚሰጠው ስልጠና በአንድ በኩል የደረጃ ማሻሻያ በሌላ በኩልም በሙያ ማሻሻያ መርሃ ግብሮች ተከፍሎ የሚፈፀም ነው። የደረጃ ማሻሻያው ስልጠና ከሰርቲፊኬት ወደ ዲፕሎማ፣ ከዲፕሎማ ወደ መጀመሪያ ዲግሪ እንዲሁም ወደ ሁለተኛ ዲግሪ እያለ በመደበኛና በርቀት ሲሰጥ ቆይቷል። ከፍተኛ ወጪ በማውጣትም በርካታ መምህራን የትምህርት ደረጃቸውን በማሻሻል ብቁ እንዲሆኑ ጥረት ተደርጓል። ስራው በቀጣይም ተጠናክሮ የሚቀጥል ይሆናል።
የመምህራንን የኑሮ ሁኔታ ከአጠቃላይ አገራዊ ኢኮኖሚው ጋር ተያያዞ መለወጡ እንደተጠበቀ ሆኖ መንግስት የመምህራንን ኑሮ ለማሻሻል የአገሪቱ አቅም የፈቀደውን ለማድረግ ጥረት ሲያደርግ ቆይቷል። ይህንኑ አጠናክሮ መቀጠል እንዳለበትም ይገነዘባል።
የተከበራችሁ የአገራችን ህዝቦች፤
በአጠቃላይ በትምህርት ዘርፍ የተመዘገቡ ስኬቶች አልጋ በአልጋ የተገኙ ሳይሆን በርካታ ችግሮችን በማለፍ ነው፡፡ አሁንም ትኩረት ሰጥተን መፍታት ያሉብን ችግሮች እንዳሉም ኢህአዴግ ይገነዘባል፡፡ የቅድመ መደበኛ፣ የጎልማሶች ትምህርት እና የልዩ ፍላጎት የትምህርት ተደራሽነትን ማሻሻል ትኩረት ከሚሹ ጉዳዮች ይጠቀሳል፡፡ የትምህርት የጥራት ፓኬጆችን አጠናክሮ በማስቀጠል በጥራት ላይ የሚታዩ ችግሮችን ደረጃ በደረጃ እየፈቱ መሄድም እንደዚሁ ትኩረት የሚሻው ጉዳይ እንደሆነ ኢህአዴግ ተገንዝቦ በመንቀሳቀስ ላይ ይገኛል፡፡
በአንጻሩ የአገራችን ተቃዋሚዎች ከፍተኛ ስኬት እያስመዘገበ የሚገኘውን የትምህርት ፖሊሲ በጭፍኑ በመቃወም ሲያጥላሉት ይታያል፡፡ ውግንናቸው ለአብዛኛው ህዝብ ባለመሆኑ የትምህርት ማስፋፋት ስራወቻችንን ሊያጣጥሉ ይፈልጋሉ፡፡ ብዙዎቹ ተቃዋሚዎች ዜጎች በአፍ መፍቻ ቋንቋ የመማር መብታቸውን ጭምር ይቃወማሉ፡፡ የኢህአዴግ ፖሊሲና ስኬቶችን ከማብጠልጠል የዘለለ ግልጽ የፖሊሲ አማራጭም አያቀርቡም፡፡
በኢህአዴግ አመራር የአገራችን ህዝቦች በትምህርት ዘርፍ የተጎናጸፉት ስኬት ተቃዋሚዎች እንደሚያጣጥሉት ሳይሆን በሁሉም መስፈርቶች ሲታይ በጣም ከፍተኛ ነው፡፡ ኢህአዴግ  ትምህርት ለአገራችን ህዳሴ ያለውን ፋይዳ በመገንዘብ ከፍተኛ ትኩረት ሰጥቶ በመንቀሳቀስ ላይ ይገኛል፡፡ በቀጣም አጠናክሮ ይቀጥላል፡፡ ኢሕአዴግ ከአጠቃላይ ትምህርት ዘርፍ በተጨማሪ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማትና በቴክኒክና ሙያ ስልጠና ተቋማትም በስርጭት፣ በተሳትፎና ጥራት ማስጠበቅ አመርቂ ድሎችን አስመዝግቧል፡፡ በእነዚህ የትምህርት መስኮች የተመዘገበውን ስኬት በሚቀጥለው የምርጫ ቅስቀሳ ዝግጅታችን የምንመለስበት ይሆናል።

የተጀመረውን የህዳሴ ጉዞ ዳር ለማድረስ ኢህአዴግን እንምረጥ!

Tuesday, April 28, 2015

የመልካም አስተደዳር ስኬቶችን በማጎልበት ድክመቶችን በማረም ለቀጣይ ለውጥ የተዘጋጀ ድርጅት - ኢህአዴግ

የተከበራችሁ የሃገራችን ህዝቦች
ኢህአዴግ መልካም አስተዳደር በሃገራችን ፈጣን ልማት ለማረጋገጥና የዴሞክራሲያዊ ስርአት ግንባታ ሂደታችንን ለማሳካት ወሳኝ ቅድመ ሁኔታ መሆኑን አበክሮ ይገነዘባል። ልማት፣ ሰላም ዴሞክራሲና መልካም አስተዳደር ለሃገራችን ህዝቦች ለምርጫ የማይቀርቡ የህልውና ጉዳዮች መሆናቸውንም በፅናት ያምናል። መልካም አስተዳደርን ማረጋገጥ ልማታችንና ለዴሞክራሲያችን ወሳኝ ቅድመ ሁኔታ መሆኑን አበክሮ ይገነዘባል፡፡ ለዚህም ነው ድርጅታችን ባለፉት ሁለት አስርተ አመታት ልማት፣ ሰላም፣ ዴሞክራሲና መልካም አስተዳደርን አጣምሮ ተግባራዊ በማድረግ የሃገራችንን ገፅታና የዜጐቿን ህይወት በመቀየር ላይ የሚገኘው።
በአገራችን ተጨባጭ ሁኔታ የምንገነባው ዴሞክራሲያዊ ስርአት የመልካም አስተዳደር መርሆዎችን አሟልቶ ተግባራዊ ማድረግ እንደሚገባ ኢህአዴግ በፕሮግራሙ በግልጽ አስቀምጧል፡፡ መልካም አስተዳደር በአለም አቀፍ ደረጃ ተቀባይነት ያላቸው መርሆዎች ያሉት ሲሆን ዋና ዋናዎቹም የህዝብ ተሳትፎና ፍትሃዊ ተጠቃሚነት፣ የህግ የበላይነት፣ ግልጽነትና ተጠያቂነት እንዲሁም ቀልጣፋነትና ውጤታማነት ናቸው፡፡
በአገራችን እነዚህ መሰረታዊ የመልካም አስተዳደር መርሆዎች ባለፉት ስርአቶች ፈጽመው የማይታሰቡና የተገደቡ ነበሩ፡፡ በነገስታቱ ዘመን በህገ መንግስታቸው ጭምር ነገስታቱን መውቀስም መክሰስም እንደማይቻል የተደነገገበትና “ንጉስ አይከሰሰም ሰማይ አይታረስም” በሚል መርህ የመሪዎች ግልፀኝነትና ተጠያቂነት ፈጽሞ የማይጠበቅበት ሁኔታ ነበር። በወታደራዊው የአገዛዝ ዘመንም አስተዳዳሪዎችን መቃወም፣ በፈለጉት አግባብ ተደራጅቶ የተለያዩ ሃሳቦችን ሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ በሆነ መንገድ መግለፅ ቀርቶ ልዩነትን ማሰብ በራሱ በጸረ አብዮተኛነት አስፈርጆ ህይወት ያሳጣ ነበር። ይህ ታሪካዊ እውነታ የሚነግረን በነገስታቱም ሆነ በወታደራዊ አምባገነኖቹ የአገዛዝ ዘመን የአገራችን የመልካም አስተዳደር ችግር የጀመረው ዴሞክራሲን በማፈንና በመርገጥ እንደነበር ነው።
በአንፃሩ በኢህአዴግ መሪነት እተገነባ የሚገኘው ልማታዊና ዴሞክራሲያዊ ስርአታችን በሃገራችን መልካም አስተዳደር እንዲሰፍን በትጋት መስራት የጀመረው የዜጐችን የዴሞክራሲና የሰብአዊ መብት ጥያቄዎች በአግባቡ በመመለስ ነው። በሃገራችን ልዩ ነባራዊ ሁኔታ በእርግጥም የአፈናና ስርአቱ እንደተገረሰሰ ህዝቡ ውስጥ ለዘመናት ሲብላሉ የቆዩትን የዴሞክራሲ ጥያቄዎች ሳይመለሱ ልማትም ሆነ መልካም አስተዳደር በቅጡ ሊጀመር ይቅርና ሊታሰብ አይችልም ነበር። በዚህ ምክንያት ልማታዊና ዴሞክራሲያዊ ስርአታችን ፈጣኑን ልማትም ሆነ ስለመልካም አስተዳደር ማሰብ የጀመረው ለህዝቦች የዴሞክራሲና የሰብአዊ መብት ጥያቄዎች አስተማማኝ ምላሽ በመስጠት ነው። ይህም በመሆኑ ለመልካም አስተዳደር ወሳኝ ቅድመ ሁኔታ የሆነው የህዝቦችንና የዜጎችን መሰረታዊ መብቶችና ነጻነቶች ዋስትና የሚሰጥ ህገ መንግስታዊ ስርአት መኖሩ እንዲሟላ አድርጓል፡፡
የተከበራችሁ  የአገራችን ህዝቦች
የህግ የበላይነት የዴሞክራሲያችን አንዱ ምሰሶ መሆኑን በማመን ኢህአዴግ በመስመሩና በፖሊሲዎቹ በግልጽ አስቀምጦ ለተግባራዊነቱ ተረባርቧል፡፡ ያለአግባብ መጠቀም ያለንን ውስን ሃብት ለልማት ለማዋል እንዳንችል እንቅፋት የሚፈጥር መሆኑንና ተጠያቂነት የሚያስከትል አሰራር መከተል እንደሚያስፈልግም ይገነዘባል። በእስካሁኑ ጉዟችን የታዩ የመልካም አስተዳደር ስኬቶችና እጥረቶችን አለም አቀፍ ተቀባይነት ያላቸውን የመልካም አስተዳደር መርሆዎች መሰረት አድርጎ በሚዛኑ መመልከት ጥንካሬዎቻችን አጠናክረን እጥረቶቻችን አርመን ለቀጣይ ለውጥ እንድንተጋ የሚያስችል ነው፡፡ ከዚህ አንፃር ድርጅታችን ኢህአዴግ ከህዝቦቻችን ጋር በመሆን በ24 አመታት ጉዟችን በመልካም አስተዳደር ስኬቶችን ያስመዘገበውን ያህል ገና ያልፈታናቸው እጥረቶች እንዳሉም ይገነዘባል፡፡ እነዚህን የመልካም አስተደዳር ስኬቶችን አጠናክሮ ለመቀጠልም ሆነ እጥረቶችን ለማረም ታዲያ ህዝቡ ወሳኝ ሚና እንዳለውም ኢህአዴግ በጽናት ያምናል፡፡ ያለ ህዝብ ተሳትፎ ዴሞክራሲና ልማት ማምጣት እንደማይቻል እንዲሁም የህዝብ ተጠቃሚነት ያላረጋገጠ ዴሞክራሲና ልማት ዘላቂነት እንደሌለው ኢህአዴግ ከጅምሩ አቋም የወሰደበት ጉዳይ ነው፡፡
የህዝብ ተሳትፎና ፍትሃዊ ተጠቃሚነት መልካም አስተዳደር ከሚለካባቸው መንገዶች አንዱ ነው፡፡ ለዚህም ነው የኢህአዴግ ሁሉም ፖሊሲዎቹ ዋነኛ ማእከል የህዝብ ተሳትፎና ተጠቃሚነት የሆነው፡፡ በአገራችን ከፍተኛ የህዝብ ተሳትፎ ከተረጋገጠባቸው ጉዳዮች ውስጥ አንዱ የኢፌዲሪ ህገ መንግስትን የማርቀቅና የማጽደቅ ሂደት ነበር፡፡ የህገ መንግስቱ የማርቀቅና የማጽደቅ ሂደት ካለፉት ስርአቶች ህገ መንግስቶች በእጅጉ በተለየ ሁኔታ ከፍተኛ የህዝቦች ተሳትፎና ባለቤትነት የተረጋገጠበት ነበር፡፡ ሁሉም ህብረተሰብ በየአካባቢው በመሰረታዊ የህገ መንግስቱ ጉዳዮች በቀረቡ አማራጮች ላይ ተወያይቶ ድምጽ እንዲሰጥበት ተደርጓል፡፡ የህዝቡን ፍላጎቶች መሰረት ተደርጎ በተዘጋጀው ረቂቅም ህዝቡ በዴሞክራሲያዊ መንገድ ተወካዮቹን መርጦ የህገ መንግስት ጉባኤ ተቋቋሞ ጥልቀት ያለው ውይይት ካደረገ በኋላ ህገ መንግስቱ ጸድቋል፡፡ የአገራችን ህዝቦች በከፍተኛ ተሳትፎና ባለቤትነት ያጸቁት ህገ መንግስት ከሌሎች የዴሞክራሲ አገራት ከተለመደው የውክልና ተሳትፎ በተጨማሪ ቀጥተኛ ተሳትፎንም አካቶ ይዟል። ይህም የሚያሳየው በአገራችን በመገንባት ላይ የሚገኘው ስርአት ከጅምሩ የህዝብ ተሳትፎና ባለቤትነት የተረጋገጠበት መሆኑን ነው፡፡
ኢህአዴግ የህዝብ ተሳትፎ ለእውነተኛ ለውጥ ግብአት የሚሆነው የነቃ፣ ነፃና የተደራጀ ሆኖ ሲፈፀም ብቻ መሆኑን አጥብቆ ያምናል። በመሆኑም ድርጅታችን የህዝቡ ተሳትፎ በነፃ ፍላጐትና ውሳኔ ላይ የተመሰረተ መሆን እንዳለበት በሁሉም ፖሊሲዎቹና ስትራቴጂዎቹ አስቀምጧል። በተግባርም ባለፉት ሁለት አስርተ አመታት የህዝቡ ተሳትፎ ንቁ፤ ነፃና የተደራጀ እንዲሆን ብዙ ሰርቷል። ይህም በመሆኑ ነው ኢህአዴግና የሚመራው መንግስት ያወጧቸውን ፖሊሲዎችና ስትራቴጂዎች ወደ ተጨባጭ እቅድ በመቀየር ተጨባጭ ስኬት ማስመዝገብ የተቻለው፡፡ ባለፉት 12 አመታት በአገራችን የተመዘገበው ፈጣንና ህዝቡን በየደረጃው ተጠቃሚ እያደረገ የሚገኘው የኢኮኖሚ እድገት ከትክክለኛ ፖሊሲና ከከፍተኛ የህዝብ ተሳትፎ ውጪ ሊታሰብ እንኳን የሚችል አይደለም።
በገጠር አርሶ አደሩ አካባቢያዊ እውቀቱን፣ ጉልበቱንና የተፈጥሮ ሃብቱን አዋህዶ ጥቅም ላይ በማዋል በግብርና ልማታችን ላይ ታይቶ የማይታወቅ እመርታ አስመዝግቧል። ባለፉት አመታት አርሶ አደሩ በተፋሰስ ልማትና በአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራዎች ላይ ያፈሰሰው ጉልበትና ያስገኘው ውጤት የሃገራችንን ታሪክ የሚቀይር ተጨባጭ አቅም ሆኗል። ከተሞቻችን አፍርሰን ዳግም የመገንባት ያህል እያካሄድን ባለነው ሁለገብ የልማት ርብርብ ውስጥ የነዋሪዎቹ የገንዘብና የጉልበት አስተዋፅኦ መንግስት ከሚመድበው መዋእለ ነዋይ የማይተናነስ እየሆነ መጥቷል። በገጠርና በከተሞች ባለፈ ታሪካችን ከጥቅም ርቀው የቆዩት ሴቶችና ወጣቶች በሁሉም መስክ በተደራጀ መንገድ እየተሳተፉ የስርአቱ ተጠቃሚ መሆን ጀምረዋል።  ባለፉት ጥቂት አመታት ደግሞ በልማት ሰራዊት እና በሌሎች የህዝብ አደረጃጀቶች አማካኝነት በገጠርና በከተማ የህዝቡን የተደራጀ ተሳትፎ ለማረጋገጥ ከፍተኛ ጥረት አድርገናል። በሂደቱም አመርቂ ውጤት አግኝተናል።
በትክክለኛ ፖሊሲ፣ ብቃት ባለው አመራርና በህዝብ ሁለንተናዊ ተሳትፎ ባለፉት ሁለት አስርት አመታት የተመዘገቡ የልማት ስኬቶች የተረጂነት ቁጥር በእጅጉ እንዲቀንስ በማድረግ፣ በርካታ ዜጎች ከእጅ ወደ አፍ ኑሮ ወጥተው ሃብት ማፍራት መጀመራቸው እንዲሁም የመሰረት ልማትና የማህበራዊ ልማት ለአብዛኛው ህዝብ ተደራሽ ለማድረግ የተሰሩ ስራዎች የህዝብን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ናቸው፡፡ በእነዚህ አመታት የተገኙ ስኬቶች አገራችን ከነበረችበት አስከፊ ድህነት፣ ኋላቀርነትና የሰላም እጦት አኳያ ሲታይ በቀላሉ የማይታዩና ለወደፊቱም ድህነትን አስወግደን የሁሉም ዜጎች ተጠቃሚነት በሚፈለገው ደረጃ ለማረጋገጥ እንደምንችል ብሩህ ተስፋ የፈነጠቁ ሆነዋል፡፡
ኢህአዴግ የህዝብ ተጠቃሚነትን በማረጋገጥ ረገድ በእስካሁኑ ስኬቶች ተኩራርቶና ረክቶ የሚቆም ሳይሆን የህዝቦችን ተጠቃሚነት በተሟላ ሁኔታ ለማረጋገጥ ከምንጊዜውም በላይ በትጋትና በቁርጠኝነት መስራት እንደሚገባው ያምናል፡፡ በአገራችን አሁንም ድህነት ሙሉ በሙሉ ያልተወገደ በመሆኑ በድህነት ውስጥ የሚኖሩ ዜጎች መኖራቸውን፣ አሁንም ስራ ያልያዙ ወጣቶች መኖራቸውን እንዲሁም የመሰረተ ልማትና የማህበራዊ ልማት ጥራቱን ጠብቆ ለሁሉም ያልተዳረሰ መሆኑን ይገነዘባል፡፡ ኢህአዴግና የአገራችን ህዝቦች እነዚህን ችግሮች የመቅረፍ ብቃት እንዳላቸው ያለፉት ስኬቶቻቸው ዋነኛ ማረጋገጫዎች ናቸው፡፡ የእስካሁኑ ጉዟችን የሚያሳየው አሁንም ጠንክረን ከሰራን የማንፈታው ችግር እንደማይኖርና በድህነት ላይ የጀመርነውን ትግል በድል እንደምንወጣ ያሳያል፡፡
የተከበራችሁ የአገራችን ህዝቦች፣
ግልፅነት፣ ተጠያቂነት የህግ የበላይነትና ቀልጣፋ የመንግስት አገልግሎት ከህዝቦች ተሳትፎና ፍትሃዊ ተጠቃሚነት በተጨማሪ የሚታዩ አለም አቀፍ የጋራ ተቀባይነት ያላቸው የመልካም አስተዳዳር መመዘኛዎች ናቸው። በዚህ ምክንያት ህገ-መንግስታችን የመንግስት አመራርና አሰራር ለህዝቡ ግልፅ እንዲሆን ደንግጓል። በህገ-መንግስቱ መሰረት መንግስት በህዝብ ይጠየቃል። ዜጐች በቀጥታና በምርጫ በሚያደራጇቸው የህዝብ ምክር ቤቶች አማካኝነት መንግስትን ይቆጣጠራሉ።
በድርጅታችን የሚመራው ልማታዊ ዴሞክራሲያዊ መንግስታችን የዜጐችንና የመንግስት ግንኙነት በግልፅነትና በተጠያቂነት መርሆዎች ላይ የተመሰረተ እንዲሆን  አበክሮ ሰርቷል። በሃገራችን የመጀመሪያው በህዝብ የተመረጠ መንግስት ስልጣን ከያዘ ከ1987 ጀምሮ ህግ አውጪ፣ ህግ ተርጓሚና አስፈፃሚ በመባል የሚታወቁት ሦስቱ የመንግስት አካላት የየራሳቸውን ህገ-መንግስታዊ ተልእኮ በግልፅነትና በተጠያቂነት መንፈስ መፈፀም በሚችሉበት ሁኔታ ተደራጅተዋል። እነዚህ አካላት በተለይም ደግሞ ከተሃድሶ በኋላ አንዱ ሌላውን በብቃት መደገፍና መቆጣጠር በሚችሉበት መንገድ እንዲጠናከሩ ሆነዋል። ዛሬ በመላ ሃገራችን ከቀበሌ እስከ ፌደራል ፓርላማ በተደራጁ የህዝብ ምክር ቤቶች ውስጥ ከ4 ሚሊዮን የማያንሱ ዜጐች  ይሳተፋሉ። ድርጅታችን በየደረጃው በተደራጁ የህዝብ ም/ቤቶች በተለይም ደግሞ በቀበሌና በወረዳ ምክር ቤቶች ውስጥ የዜጐች ተሳትፎ በዚህ ደረጃ እንዲሰፋ ያደረገው የህዝቡን የመወሰን አቅም ከፍ ለማድረግና በተባበረ አቅም አስፈፃሚውን የመቆጣጠር ጉልበት እንዲኖረው ለማስቻል ነው። በዚህ ምክንያት በአሁኑ ወቅት ም/ቤቶች የዴሞክራሲያዊ ስርአት ግንባታ ሂደቱ የሚመራባቸውን ህጐች ያወጣሉ፣ እቅዶችን በብቃትና በጥራት ለማስፈፀም የሚያስችለውን በጀት ያፀድቃሉ። የህዝቡ የተናጠልና የተደራጀ እንቅስቃሴ የሚመራው ምክር ቤቶቹ በሚያወጧቸው አቅጣጫዎች ነው። አስፈፃሚ አካላት ከላይ እስከታች ለም/ቤቶቹ ወቅቱን የጠበቀ ሪፖርት ያቀርባሉ። በየደረጃው በተደራጁ ፍርድ ቤቶች ውስጥ ተመድበው የሚያገልግሉ ዳኞች የሚሾሙትና የሚሻሩትም በምክር ቤቶቹ ነው። በዚህ ሳቢያ በየደረጃው ያሉ ምክር ቤቶች የሁሉም የመንግስት አካላት የበላይና የህዝቡ የሉአላዊነት መገለጫ ሆነው እየሰሩ ናቸው።
በድርጅታችን የሚመራው ልማታዊ ዴሞክራሲያዊ መንግስታችን በየደረጃው የተደራጁ የህዝብ ም/ቤቶች በህገ-መንግስታችን የተጣለባቸውን ይህንን ከባድ ሃላፊነት በብቃት ሲወጡ የልማትና የዴሞክራሲያዊ ስርአት ግንባታ ሂደቱ ተደማሪ ስኬቶችን እያስመዘገበ ይቀጥላል ብሎ ያምናል። የህዝብ ምክር ቤቶች በሁሉም የመንግስት አካላት ላይ ተፅዕኖ ማሳደር ሲችሉ የመልካም አስተዳደር ችግሮች እየተቀረፉ እንደሚሄዱም በአፅንኦት ይገነዘባል። ከዚህ በመነሳትም የህዝብ ምክር ቤቶች በአመራር፣ በአደረጃጀትና በአሰራር ከጊዜ ወደ ጊዜ እንዲጠናከሩና በዕለት ተዕለት አፈፃፀማቸው ውጤታማ እንዲሆኑ በልዩ ትኩረት ሰርቷል። ምክር ቤቶቹ ባለፉት አምስት አመታት አስፈፃሚውን ለመደገፍና ለመቆጣጠር ያሳዩት ተነሳሽነትና የተገኘው ተጨባጭ ውጤት የዚህ ማሳያ ነው።
 የተከበራችሁ የሃገራችን ህዝቦች
በየትኛውም መንግስት የአመራርና የአሰራር ሂደት ውስጥ የአገልግሎት ቅልጥፍናና ፍትሃዊነትን በማዛባት ስርዓቱንና ህዝቡን ለመልካም አስተዳደር ጉድለትና ለብልሹ አሰራር  ከሚያጋልጡ ችግሮች አንዱ ሙስና ነው። ድርጅታችን እየገነባን ላለነው ልማታዊና ዴሞክራሲያዊ ስርአት ዋነኛ አደጋ በማንኛውም አጋጣሚና የስራ ሂደት ውስጥ እሴት ሳይጨምሩ የመጠቀም ወይም የኪራይ ሰብሳቢነት ችግር መሆኑን ለይቶ የሞት ሽረት ትግል ከጀመረ አመታት ተቆጥረዋል። በተለይም ባለፉት አምስት አመታት ስርአታችንን ለኪራይ ሰብሳቢነት የሚያጋልጡት የስራና የስምሪት መስኮች ተለይተዋል። የገጠርና የከተሞች የመሬት አስተዳደርና አጠቃቀም፣ የግዢ ስርአታችን እንዲሁም የግብር አስተዳደር እና የንግድና የኮንስትራክሽን ዘርፎች መሆናቸውን ለይቶ ውጤታማ ትግል አካሂዷል። በመሆኑም በከተሞች የመሬት አስተዳደርና አጠቃቀም ዙሪያ የሚታየውን ህገ-ወጥ ወረራና የሙስና ችግር ለመቅረፍ የተዘጋጀው አዲሱ የሊዝ አዋጅ አመርቂ ውጤት አስገኝቷል። በሌሎቹ የስራ ዘርፎች እየተወሰዱ ያሉ ቀጣይነት ያላቸው የማሻሻያ እርምጃዎችም ለውጤት እየበቁ ናቸው።
ሙስናን አስተማማኝ በሆነ መንገድ መዋጋት የሚቻለው በአመራሩና በአጠቃላይ ህዝቡ ዘንድ በሚፈጠር የአስተሳሰብ ለውጥ ነው። ድርጅታችን ሙስናን የልማታችንና የዴሞክራሲያዊ ስርአት ግንባታችን እንቅፋት በማይሆንበት ደረጃ ማስወገድ የሚቻለውም የህዝቡን ሁለገብ ተሳትፎ በማረጋገጥ እንደሆነ ያምናል።  ሙስናን በመከላከል ሂደት የህዝቡን ተሳትፎ አሟልቶ ማረጋገጥ የሚቻለውና ትግሉ ለፍሬ የሚበቃው ደግሞ ሙስናን የሚጠየፍ ህብረተሰብ በመገንባት እንደሆነ አበክሮ ይገነዘባል። ስለሆነም ባለፉት ሁለት አስርተ አመታት ስራ ላይ በዋለው የትምህርትና ስልጠና ፖሊሲ በተቀረፀው የስነ-ዜጋና የስነ-ምግባር ትምህርት አማካኝነት በተለይም አገር ተረካቢ በሆኑ ህፃናትና ወጣቶች ላይ ውጤታማ አስተምህሮ ሰርቷል።
በስርአታችን ውስጥ በዚህ መልክ የሚካሄደውን የአስተሳሰብ ትግል እንደተጠበቀ ሆኖ ሙስና ተከስቶ ሲገኝም አጥፊዎችን ለህግ የማቅረብና የማስቀጣት ስራችን የመከላከል ስራውን በሚያግዝ መልኩ እየተፈፀመ ነው። በድርጅታችን የሚመራው ልማታዊ ዴሞክራሲያዊ መንግስታችን በሙሰኞች ላይ ጠንካራ እርምጃ ከመውሰድ ተቆጥቦ አያውቅም። በዚህ መንገድ የተወሰዱ ተከታታይ እርምጃዎች በሙስና አማካኝነት የሚፈጠሩ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን እየፈታን በልማታዊ መንገድ እንድንቀጥል ከፍተኛ አስተዋፅኦ አበርክተዋል።


የተከበራችሁ የሃገራችን ህዝቦች
ኢህአዴግ ባለፉት ሁለት አስርት አመታት አለም አቀፍ ተቀባይነት ያላቸውን መርሆዎች ከህዝባዊ አላማዎቹና ከሃገራችን ልዩ ሁኔታ ጋር አጣጥሞ በስራ ላይ በማዋል ዜጐች የመልካም አስተዳደር ተጠቃሚ እንዲሆኑ ሌት ከቀን ሰርቷል፤ አሁንም እየሰራ ነው። በሂደቱም እስካሁን በዝርዝር ያየናቸው ውጤቶች በየዘርፉ ተመዝግበዋል። አሁንም በየዘርፉ የተመዘገቡት በጐ ፍፃሜዎቻችን እንደተጠበቁ ሆነው ድርጅታችን በውጤታማ የልማትና የዴሞክራሲያዊ ስርአት ግንባታ ትግላችን ውስጥ እያጋጠሙ ካሉ ፈተናዎች አንዱና ቀዳሚው የመልካም አስተዳደር ችግር መሆኑን ይረዳል። ከመሰረተ ልማት አገልግሎት አንፃር የመብራት፣ የውሃ፣ ስልክ እንዲሁም በግብርና በታክስ፣ በመንግስታዊ አግልግሎቶች እና በመሳሰሉት በህዝቡ የሚነሱ የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች መኖራቸውን ኢህአዴግ ይገነዘባል፡፡
አጠቃላይ የህዝቡ ጥያቄዎች ሲታዩ በአንድ በኩል የልማት ጥያቄ ገጽታ ያላቸውና ካለን አቅም አኳያ ደረጃ በደረጃ መፈታት የሚገባቸው ሲሆኑ በሌላ በኩል ከአመራሩና ከፈጻሚው አካል አግልግሎት አሰጣጥ መጓደል የሚከሰቱ ናቸው፡፡ መንግስት በፌዴራልና በክልሎች ደረጃ የመልካም አስተዳደር ማሻሻያ ንቅናቄ በመፍጠር እነዚህን ችግሮች ለመፍታት እየሰራ ይገኛል። የመልካም አስተዳዳር ችግር ምንጭ ተደርገው የተለዩ ተቋማት ችግሮቻቸውን የሚፈቱበት የተደራጀ እቅድ እያወጡ ወደ ስራ እንዲገቡ ተደርጓል። አንዳንዶቹ ለውጥ ማምጣት ጀምረዋል። ይሁን እንጂ አሁንም በብዙዎቹ የህዝብ እርካታ በሚፈለገው ደረጃ አልተረጋገጠም፡፡ ስለሆነም ልማትን በማፋጠን የሚፈቱትን የህዝብ ጥያቄዎች ከህዝቡ ጋር በመወያየት ቅደም ተከተል አውጥቶ መፍትሄ ለመስጠት የተጀመረው ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል።
ከልማት ጋር የተያያዙ የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች እንደተጠበቁ ሆኖ በየደረጃው ካለው አመራርና ሰራተኛ የአገልጋይነት መንፈስ መጓደልና ከኪራይ ሰብሳቢነት አመለካከትና ተግባር የሚመነጩ የመልካም አስተዳደር ችግሮች አሉ። እነዚህን ችግሮች የግልጸኝነትና የተጠያቂነት አሰራር በማጠናከርና በሂደቱም የህዝቡን የተሟላ ተሳትፎ በማረጋገጥ መፍታት ጊዜ የማይሰጠው መሆኑን ኢህአዴግ ይገነዘባል። ለዚህም ተግቶ እንደሚሰራ ሊያረጋግጥላችሁ ይወዳል፡፡
የመልካም አስተዳደር ችግሮች በተሟላ ሁኔታ የመፍታት ብቃት ያላቸው ኢህአዴግና የአገራችን ህዝቦች መሆናቸው ያለፉት ሁለት አሰርት አመታት ጉዞዎቻችን ያሳያሉ፡፡ ኢሕአዴግ በየጊዜው ከሚያስመዘግባቸው ስኬቶቹ ብቻ ሳይሆኑ ከስህተቶቹም እየተማረ ለድል የበቃ ድርጅት ነው። የአገራችን ተቃዋሚዎች ግን የመፍትሄ አካል ከመሆን ይልቅ ችግሮችን በፈጠራ ወሬዎች በማጀብ ማራገብ የቀን ተቀን ተግባራቸው ሆኗል፡፡ የአገራችን ህዝቦች በገሃድ የሚያውቁቱን እውነታ ክደው አገራችን ድቅድቅ ጨለማ ውስጥ እንደገባች አስመስለው ሲስሏት ይታያሉ፡፡ የአገራችን ተቃዋሚዎች ብዙዎቹ ካለፈው ስህተታቸው ሳይማሩ አሁንም በእራሳቸው ውስጣዊ ዴሞክራሲ ማረጋገጥ አቅቷቸው ሲተራመሱ እየዋሉ ለህዝቦች የመልካም አስተዳደር አረጋጋጭ ሆነው ለመቅረብ ይሞክራሉ። ይህም በመሆኑ የአገራችን ተቀዋሚዎች የመልካም አስተዳደር አማራጭ እንደማይሆኑ በቀላሉ ድምዳሜ ላይ መድረስ ይቻላል፡፡
ህዝባዊ ባህሪ የተላበሰው ኢህአዴግ ሁልጊዜም የውስጥ ድክመቶችን ታግሎ እያረመ አሁን አገራችን ከደረሰችበት ሁለንተናዊ ለውጥ ያደረሰ መሆኑ የአገራችን ህዝቦች የምትገነዘቡት ነው፡፡ ለዚህም ነው የመልካም አስተዳደርን በማረጋገጥ የህዝብ እርካታን አላረጋገጥኩም ብሎ ችግሩን ወደ ውስጡ የሚያየው፡፡ ለዚህም ነው በአገራችን በለውጥ ጎዳና እየተጓዘች ባለችበት በአሁኑ ጊዜ እየታዩ ያሉ ችግሮቹን ሊፈቱ የሚችሉት በኢህአዴግና በአገራችን ህዝቦች የጋራ ትግል ነው የምንለው፡፡   
ኢህአዴግን መምረጥ የህዝቡን ተሳትፎና ፍትሃዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ መልካም አስተዳደር ማስፈን ነው።
ኢህአዴግን ይምረጡ

ምልክታችን ጣፋጩን ማር የምታመርተውን ታታሪዋ ንብ ነች!!

ISIS leader declared 'clinically dead' by Israeli doctors in Golan

An encounter in March allegedly left al-Baghdadi mortally wounded, allowing Abdul Rahman al-Sheijlar, also called Abu Ala Afri to succeed him.

Following reports by Iranian and Iraqi media that Islamic State leader, Abu Bakr al-Baghdadi, had suffered critical injuries in Iraq, unsubstantiated rumors have now surfaced that al-Baghdadi has been declared "clinically dead" by Israeli physicians in the Golan Heights.

Iran's state FARS news, quoting two Iraqi media outlets, claimed that the spiritual and military leader of the self-styled caliphate had been injured in Western Iraq during an assault by Iraqi and Shi'ite forces on March 18 and that he had somehow been transferred to the Israeli Golan Heights, where surgeons and physicians had declared him clinically dead.  
 

However, various claims of how exactly al-Baghdadi was injured last month have rendered the truth elusive.  In March, the British daily, the
 Guardian quoted an Iraqi political adviser, Hisham al-Hashimi, and an unnamed Western diplomat as claiming that  al-Baghdadi suffered life-threatening injuries during a US airstrike in the Nineveh region, close to the Syrian border.

A Pentagon official, Army Colonel Steven Warren, swiftly denied that al-Baghdadi had been the target of any strike, however, telling the Daily Beast that there is "no reason to believe it was Baghdadi" who was hit by the war plane's payload.
 

In any case, the encounter apparently left him mortally wounded and unable to resume his post, a position that has been allegedly filled by a new shady figure, al-Baghdadi's successor, Abdul Rahman al-Sheijlar, also called Abu Ala Afri.

According to al-Hashimi, Afri had been a physics teacher and established academic who had penned multiple publications on topics ranging from science to religion. He had had joined al-Qaida after the American invasion however, an supervised its Iraqi branch, known as al-Qaida in Mesopotamia.

Reports from the Iranian and Iraqi media have also suggested that following the decline in al-Baghdadi's health, infighting and disputes have arisen among various factions in the Islamic State group with the group's Syria branch expressing dissatisfaction with the choice of the new leader.