Monday, August 4, 2014

ለመንግስት ሰራተኞች የደመወዝ ጭማሪ 10 ነጥብ 3 ቢሊዮን ብር መመደቡን መንግስት አስታወቀ

በዝቅተኛ የደመወዝ እርከን ላይ ለሚገኙ ሰራተኞች 46 በመቶና ለከፍተኛ ደመወዝ ተከፋዮች ደግሞ 33 በመቶ ጭማሪ እንደተደረገ የገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚንስትሩ አቶ ሱፊያን አህመድ ገልፀዋል።

በዝቅተኛ የደመወዝ እርከን ላይ ለሚገኙ ሰራተኞች 46 በመቶና ለከፍተኛ ደመወዝ ተከፋዮች ደግሞ 33 በመቶ ጭማሪ እንደተደረገ የገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚንስትሩ አቶ ሱፊያን አህመድ ገልፀዋል።

አቶ ሱፊያን ሐምሌ 26 ቀን 2006 በጽህፈት ቤታቸው በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ  እንዳብራሩት ለሰራተኞች የተደረገው የደመወዝ  ጭማሪ በዋጋ ግሽበት ላይ ምንም አይነት ተፅዕኖ አይፈጥርም።

የደመወዝ ጭማሪው ከሀምሌ 2006 ጀምሮ ተግባራዊ መሆኑን ያስታወሱት ሚንስትሩ የተደረገው ማስተካከያ ክፍያ ከነሀሴ ወር ደመወዛቸው ጋር እንደሚከፈላቸው በመግለፅ ጭማሪው በሁሉም የመንግስት እርከን ያሉ 1 ነጥብ 3 ሚሊዮን ሰራተኞችና የስራ ኃላፊዎችን እንደሚያካትት አረጋግጠዋል።

አቶ ሱፍያን እንዳሉት ለዩኒቨርሲቲ መምህራን፥ በጥናትና ምርምር ዘርፍ ለተሰማሩ ተመራማሪዎችና ለህክምና ባለሙያዎች መንግስት ልዩ የደመወዝ ጭማሪ ያደርጋል።

ከመጭው መስከረም ወር ጀምሮ የሰራተኛውን የትራንስፖርት ችግር ለመቅረፍ 420 ዘመናዊ አውቶብሶች ተገዝተው ሀገር ውስጥ  መግባታቸውን የገለፁት አቶ ሱፊያን የትራንስፖርት  አገልግሎቱ በተደራጀ ሁኔታ ለመምራት ሰራተኞች በስልጠና ላይ ናቸው ብለዋል።

ሚንስትሩ ክለውም የሰራተኛውን የመኖሪያ ቤት ችግር ለመቅረፍ የሚያስችሉ ስራዎች በመስራት ላይ መሆናቸውንም ገልፀዋል።

የሲቪል ሰርቪስ ሚንስትር ዴኤታ ዶክተር ምስራቅ መኮንን በበኩላቸው የአሁኑ የመንግስት የደመወዝ ጭማሪ መነሻ የመንግስት የመክፈል አቅም ከፍ ማለቱ ማሳያ መሆኑን አስታውሰው አጠቃላይ ፈጣን ልማቱ ተጠናክሮ እንዲቀጥልና ዝቅተኛ ኑሮ የሚኖረው የመንግስት ሰራተኛ ኑሮው እንዲሻሻል ለማድረግ ያግዛል ብለዋል።

የመንግስት ሰራተኛው በሚሰራበት አካባቢ ራሱን በማደራጀት ለኑሮው አስፈላጊ የሆኑ ሸቀጦችን ማቅረብ የሚያስችል አሰራር በመዘርጋት ላይ መሆናቸውንም ዶክተር ምስራቅ ገልፀዋል።

የአሁኑ የደመወዝ ጭማሪ ጠቅላይ ሚንስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ ሰኔ 16 ቀን 2006 ሀገር አቀፍ የሲቪል ሰርቪስ ቀን ሲከበር መንግስት ለሰራተኛው የደመወዝ ጭማሪ እንደሚያደርግ ቃል መግባታቸውን ተከትሎ  የተደረገ ሲሆን ሀምሌ 25 ቀን 2006 የሚንስትሮች ምክር ቤት የደመወዝ ጭማሪውን እንዳፀደቀውም ሂደቱን ለህዝብ ይፋ ማድረጋቸውን አስታውቀዋል።


ንጭ
http://www.eprdf.org.et/web/guest/home/-/asset_publisher/6RcW/content/sivilcervice-empeeloy-salery-increment-news-4-agu-2014 

No comments:

Post a Comment